“ከኢህአዴግ ጋር ብዙ ጊዜ ተደራድረናል፣ 101 ጊዜ ከድቶናል!”

“እኔ እዚያ ውስጥ ባልገባ ደስ ይለኛል። እኔ እሳቸው (ኃይሉ ሻውልን) ፖለቲካ አውቀው እንዲህ ይበሉ አይበሉ አላውቅም። ምን ትርፍ እናመጣለን ብለው እዚያም ውስጥ እንደገቡ አላውቅም። ለምን ብቻቸውን ተነጥለው እዚያው ውስጥ እንደገቡ እሳቸውን ብትጠይቁ ይሻላል። እነዚያ መሠረታዊ ጉዳዮች ሳይመለሱ ዋስትና ሳይሰጥ መግባታቸው ምክንያቱ አልገባኝም። እናውቀዋለንኮ። ከኢህአዴግ ጋር ብዙ ጊዜ ተደራድረናል፣ 101 ጊዜ ከድቶናል። ለማንኛውም ነገሩኮ ውሎ ሳያድር በሳምንትና ወራት ጊዜ ውስጥ ይታወቃል። ኢህአዴግኮ ካላሳረ፣ ካላባረረ የኢትዮጵያን ህዝብ ማስተዳደር ከማይችልበት ደረጃ ደርሷል። ይህን እሳቸውም ያውቃሉ፣ እኛም እናውቃለን። እሳቸው እንደሚሉት ታሪካዊ ክንዋኔ ይሁን ሌላ ይሁን ወደፊት እናየዋለን። ፍቅራቸው እንደዚያ ይቀጥል ዳግመኛ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ቲአትር ለመስራት ይሁን በቀናት ውስጥ እናየዋለን። እኛኮ ኢህአዴግ እሳቸው እንደሚሉት ቢሆን ቢያደርግ ደስ ይለናል። ኢህዴግን የሚያውቁ የኢህአዴግ መሪዎች የነበሩኮ እኛጋ አሉ!”
ዶ/ር መረራ ጉዲና (ለማንበብ)

Leave a Reply

Photo Gallery

Designed by Nebxstudios